የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሰራተኞች 12ኛውን የኢትዮጵያ ብሄሮች፤ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በተቋም ደረጃ አከበሩ፡፡ በዓሉ‘’ በሕገ-መንግስታችን የደመቀ ሕብረ-ብሄራዊነታችን ለህዳሴያችን!’’ በሚል መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን የመወያያ ፅሁፉ በአቶ ዋሲሁን ዓለማየሁ የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ቀርቧል፡፡
የተዘጋጀው የመወያያ ሰነድ ዋነኛ ትኩረቶች፡ –
የፌዴራል ስርዓት
- የፌዴራሊዝም ታሪካዊ አመጣጥና መነሻ
- የፌዴራሊዝም ስርዓትን መከተል ያለው ፋይዳ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮ አንፃር
- የፌዴራል ስርዓቶች የሚጋሩዋቸው መሰረታዊ ባህርያት
- በእኛ ሀገር ነባራዊ ሁኔታ ልማትና ዴሞክራሲ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ መሆናቸው
- በህብረ-ብሄራዊ የፌዴራል ስርዓት መVላት የሚገባቸው
- ዴሞክራሲ ፣
- ሕገመንግስታዊነት፣
- የመድብለ -ፓርቲ ስርዓት መኖር፣
- በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ የህዝቦች ህብረት መኖር፣
- የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ፣
- የአናሳ ቡድኖች (Minorities) ድምፅ መሰማት፣
- አብሮነትና ብዙህነትን ማቀፍ፣
- የመንግስታት ግንኙነት መኖር …. ወዘተ
በሀገር ደረጃ የፌዴራል ስርዓቱ ያስገኛቸው ስኬቶች…
- የሰብአዊና የዲሞክራሲያዊ መብት ጥያቄዎችን የመለሰ ስርዓት መሆኑ፣
- አንድነት ያስቀጠለ ስርዓት መሆኑ፣
- የመድብለ ፓርቲን ስርዓትን ዕውን ያደረገ ስርዓት መሆኑ፣
- ከ10 ዓመታት በላይ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ማስመዝገብ የቻለ ስርዓት መሆኑ፣
- የማህበራዊና መሰረተ ልማት አውታሮች ልማት እያረጋገጠ የሚገኝ ስርዓት መሆኑ፣
- በአጠቃላይ በማህበራዊ፤ኢኮኖሚዊና ፖለቲካዊ መስኮች ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑ፡፡
የፌዴራል ስርዓቱ ላይ እያጠሉ ያሉ እሳቤዎችና ተግባራት
- በሕገ-መንግስታችን ዙሪያ የጋራ አረዳድና ግንዛቤ በሚፈለገው ደረጃ አለመኖር፤
- የትምክህትና ጠባብ አስተሳሰብ የወለዳቸው ችግሮች አሁንም ያልተፈቱ መሆን፤
- የሃይማኖት አክራሪነት
- የኪራይሰብሳቢነት አዝማሚዎችና ተግባራት
- የኮንትሮባንዲስቶች እንቅስቃሴ መኖር
- ከአስተዳደር ወሰንና መሰል ጉዳዮች ጋር ተያይዞ አልፎ አልፎ ግጭቶች መከሰታቸው
ቀጣይ አቅጣጫዎች
1) የመከባበር ፣ መደማመጥ፣ መቻቻል፣ መደጋገፍ፣ መተባበር ባህልን ማጎልበት ፣ብዙህነትን ማክበር፣
2) የጋራ ማንነት መገለጫዎችን ማጎልበት፣
3) የመንግስታትና የህዝቦች ግንኙነቶችን ማጠናከር፣
4) ሕገ-መንግስትና ሌሎች የስርዓቱ ሕጎችን ማክበርና መጠበቅ፣
5) ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ መላ ሃብትን ማነቀሳቀስና መረባረብ፣
6) ጎጂ የውጭ ፖለቲካን (Imported Politics) ማስወገድ፣
በቀረበው ሰነድ መነሻነት ከወቅታዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች፤በተለይም ከፌዴራል ስርዓቱ ጋር ተያይዞ በውይይቱ ተሳታፊ የነበሩ ሰራተኞች ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ያቀረቡ ሲሆን፤ ውይይቱን የመሩት አቶ ዋሲሁን ዓለማየሁ እና ወ/ሮ ገንዘቤ ተስፋዬ የኢንስቲትዩቱ የሰው ሀብት ስራ አመራር ዳይሬክተር ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም የፌዴራላዊ ስርዓቱን አደጋዎች ጠንቅቆ በማወቅ በየጊዜው መልካቸውን እየቀየሩ የሚመጡ ችግሮችን የኢንስቲትዩቱ ሰራተኞች በጋራ መታገል እንደሚገባቸው መግባባት ላይ በመድረስ የበዓሉ ፍፃሜ ሆኗል፡፡
You must be logged in to post a comment.